እልል ያለ ሽልማት
እልል ላለ ሽልማት የታጫችሁት ሁሉ እንኳን ደስ አላችሁ!
ጊዜና ታሪክ እራሳቸውን የሚያኖሩበት፣ በከበሩ ድንጋዮች የታነጸ ውብ ሕንጻ ነው - ባህል ማለት። የከበሩ ድንጋዮች በዘመናት ሂደት ውስጥ ማንነታችውን ሳይለቁ ወሳኙን ለውጥ በማስተናገድ ለየት ብለው እንደሚያሸበርቁት ሁሉ ባህልም ሥር መሠረቱን ሳይለቅ ከአዳዲሱ ጋር እየተናበበ እና እየተዋሃደ የየዘመኑንም መልክ እያተመ ይጓዛል። እንዲህ በከበረ ድንጋይ ተምሳሌት ያዘጋጀነው ሽልማትም የምንጋራው ባህልና ታሪካችን ዘመናትን በጽናት የሚሻገር መሆኑን ይመሰክራል።
አቶ ፍቃዱ ዋሬ በሙዚቃ
ኢንዱስትሪ ዘርፍ የመጀመሪያው ዙር የእልል ያለ ሽልማት የህይወት ዘመን ተሸላሚ ሆነው ተመርጠዋል፡፡
ባላቸው የስራ ዘመን ሙዚቃን አንዱ የጥበብ መንገድ አደጋጐ በመጠቀም የኢትዮጲያን ህብረ ብሄራዊ ባህሎች እና እሴቶች በሀገር ውስጥና ለተቀረው የዓለም ክፍል በማሳተምና በማከፋፈል ባህልንና ጥበብን በልዩነት እንዲፀባረቅ ፤ እንዲተዋወቅ እና እንዲጎለብት ስላደረጉ የእልል ያለ ሽልማት የህይወት ዘመን ተሸላሚ ሆኑ
ባህል የትያትር እስትንፋስ ነው፡፡
ኪነ ጥበብን ተዋህደው የኢትዮጲያን ድንቅ እና ውብ ባህሎችን በሀገርም ውስጥና በዓለም ዙሪያ በልዩነት ያንጸባረቁ ፤ ያስተዋወቁ እና እንዲጎለብት በማደረጋቸው አርቲስት የሺ ተክለወልድ በኪነ ጥበብ/ ትያትር ዘርፍ የመጀመሪያው ዙር የእልል ያለ ሽልማት የህይወት ዘመን ተሸላሚ ሆነው ተመርጠዋል፡፡